Play all audios:
የአውሮጳ ሕብረት አጸፋዊ ምላሽ To play this audio please enable JavaScript, and consider upgrading to a web browser that supports HTML5 audio የአውሮጳ ኅብረት የአጸፋ ርምጃ በአሜሪካን የታሪፍ ጭማሪ ላይ አሜሪካ ከትላንት ጀምሮ
በብረት እና በአሉምንየም ምርቶች ላይ ተግባራዊ ለምታደርገው አዲሱ ታሪፍ፣የአውሮጳ ኅብረት የአጸፋ ርምጃ እንደሚወስድ አስታወቋል። የአውሮጳ ኅብረትን የንግድ ፖሊሲ የሚመራው የኅብረቱ ኮሚሽን እንዳለው አሜሪካን በብረት እና በአሉምንየም ላይ ለጣለችው የ25 በመቶ ታሪፍ ጭማሪ ፣ ኅብረቱ ከጎርጎሮሳዊው
ሚያዚያ አንድ አንስቶ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰድ ይጀምራል ብሏል። የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን ከአጸፋ ርምጃው ጋር፣ ኅብረቱ ለድርድር ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል። በጉዳዮ ላይ ከብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ ጋር ያደረግነው አጭር ቆይታ የማድመጫ ማዕቀፉን በመጫን
እንድታደምጡት በአክብሮት እንጋብዛለን። ገበያው ንጉሴ ዮሃንስ ገብረእግዚአብሄር እሸቴ በቀለ